22/10/2020
ፓስፖርት
| አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት ወይም ፓስፖርት ለማደስ ለምትፈልጉ ሁሉ
አዲስ ፓስፖርት በonline ለምታመለክቱ ተገልጋዮች ማሟላት ያለባችሁ መስፈርት በተመለከተ
የአዲስ ፓስፖርት አመልካቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው፡፡
1. ይህን አገልግሎት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ሁሉንም ሰነዶች ማዘጋጀት
ህጋዊ የቀበሌ መታወቂያ ካርድ እና የተረጋገጠ የልደት የምስክር ወረቀት/ማስረጃ
2. የሚያመለክቱት ለአስቸኳይ አገልግሎቶች ከሆነ ከሚከተሉት መካከል ቢያንስ አንዱ ሊኖርዎት ይገባል
* የሕክምና ደብዳቤ
* የትምህርት እድል እና ዲቪ
* ከተፈቀደለት ድርጅት የተጻፈ ደብዳቤ
* የውጭ ሀገር የነዋሪነት ፍቃድ
* የግብዣ ደብዳቤ
* አስቸኳይ የስራ ጉዞ
* በሀዘን/ጋብቻ ምክንያት የሚደረግ ጉዞ
3. ለአዲስ ፓስፖርት የሚከፈለውን ክፍያ ያረጋግጡ
* ለ32 ገጽ ፓስፖርት 600
* ለ64 ገጽ ፓስፖርት 2186
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍላችሁ online አድራሻ ላይ አባሪ ያደርጉታል።
N.B ~ የonline አድራሻ እስክንገልጽላችሁ በትዕግሥት ጠብቁን።
የኦንላይን አገልግሎቱ ጥቅምት 10/2013 ዓ.ም ይጀመራል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ባጋጠመ የኔትወርክ ችግር ምክንያት ሳይጀምር መቆየቱን በኤጀንሲው የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ተሬሳ ተናግረዋል፡፡
የአገልግሎት ጊዜ ያበቃ ፓስፖርት በተመለከተ ፦
የአገልግሎት ጊዜ ያበቃ ፓስፖርት ለማመልከት ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው፡፡
1. ይህን አገልግሎት ለማግኘት የሚያስፈልጉ ሁሉንም ሰነዶች ማዘጋጀት ፡
የአገልግሎት ጊዜው ያበቃው ፓስፖርት የመረጃ ገጽ ኮፒ
2. የሚያመለክቱት ለአስቸኳይ አገልግሎቶች ከሆነ የሚከተሉት የግድ ሊኖሩዎት ይገባል ፦
• የሕክምና ደብዳቤ
• የትምህርት እድል እና ዲቪ
• ከተፈቀደለት ድርጅት የተጻፈ ደብዳቤ
• የውጭ ሀገር የነዋሪነት ፍቃድ
• የግብዣ ደብዳቤ
• አስቸኳይ የስራ ጉዞ
• በሀዘን/ጋብቻ ምክንያት የሚደረግ ጉዞ
3. ለሚመርጧቸው አገልግሎቶች የሚከፈለውን የአገልግሎት ክፍያ እዚህ ላይ ያረጋግጡ>፦
• ለ32 ገጽ ፓስፖርት - 600
• ለ64 ገጽ ፓስፖርት - 2186
የኢሚግሬሽን፣ ዜግነትና የወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ
ጥቅምት 10/2013 ዓ/ም
***
👉 Telegram channel
የአገር ቤት ድምፅ - ጌጡ ተመስገን - Getu Temesgen
https://t.me/joinchat/AAAAAFHhh9ZvV8Bb8wjHbA
17/06/2020
30/05/2020
09/03/2019